የደብረጽዮን መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከቀረጥ ነጻና ትርፍ አልባ የሃይማኖታዊ ተቋም እንደመሆኗ መጠን የተመሠረተችበት ዋና ዓላማ ለምእመናን ሃይማኖታዊ አገልግሎት ለማበርከት ነው። ይሕንን ዓላማ ተቀዳሚ በማድረግ ከዚህ በመቀጠል የተዘረዘሩትን ተልዕኮዎች ተግባራዊ ታደርጋለች፤
ሀ. የደብረጽዮን መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናኗን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነትንና ሥርዓተ አምልኮን በመከተል እንዲገለገሉና እንዲያገለግሉ ታደርጋለች።
ለ. ቤተክርስቲያኗ መንፈሳዊ አገልግሎቷን ለማጠናከርና የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌለ መንግሥት በሰፊው ለማዳረስ፤ እንዲሁም አገልግሎቷን አጠናክራና አስፋፍታ የእምነታችን መሠረት ሳይለወጥና ሳይበረዝ ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ ሳታቋርጥ ትሠራለች።
ሐ. በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት እምነት መሠረት ለምእመናን የጥምቀት፣ የጋብቻ እና የፍሐት አገልግሎት ትሰጣለች።
መ. አዳጊ የ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት እምነት ተከታይ ወጣቶችን ሃይማኖታቸውን፤ ኢትዮጵያዊ ቋንቋቸውንና ባሕላቸውን በማስተማር የቤተ ክርስቲያኗ ተረካቢ ዜጋ እንዲሆኑ ታዘጋጃለች።
ሠ. በኢትዮጵያ የሚገኙ ገዳማትንና አድባራትን ትረዳለች።
ረ. በየእስር ቤቱ በተለያየ ምክንያት የታሰሩትን፤ በየሆስፒታሉ በሕመም የሚሰቃዩትን፤ ጠዋሪ ቀባሪ የሌላቸውን የደከሙ አዛውንቶችንና ችግረኞችን በተቻለ መጠን በመርዳትና፡ በማጽናናትና የአለኝታነት ድጋፍ ትሰጣለች።
ሰ. ከሌሎች የሃይማኖት ተቋማት ጋር በሰብአዊ እርዳታ ጉዳዮች ላይ በመተባበር ለማንኛውም ሕብረተሰብ እርዳታ በሚደረግበት ጊዜ በእርዳታ አሰጣጡና በሥራው ትካፈላለች፡ ትሳተፋለችም።